Amharic
(i)
47 በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል።
48 እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ።
49 እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ።
50 እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።
51 ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ።